Wednesday, June 1, 2016

በናፍቆት የሚጠበቅ

ፍጥረት ሁሉ የእግዚአብሔርን ልጆች መገለጥ በናፍቆት ይጠባበቃል። ሮሜ 8:19

ፍጥረት በናፍቆት የሚጠባበቀው ምናችንን ይሆን? በእርግጥ ይህን ጥያቄ ብዙ ጊዜ ለራሴ እጠይቃለሁ። ምናልባትም ሌሎች ሰዎችም ብዙ ጊዜ ይጠይቁ ይሆናል። አዎ በየጊዜው መልስ የሆናሉ ብዬ ያቀረብኩዋችው ብዙ ነገሮች ነበሩ። ለምሳሌ አምልኳችንን፣ ኑሯችንን፣ መውጣት መግባታችንን፣ ጽድቃችንን የመሳሰሉትን። በሁሉም መልኩ በመልካም ሁኔታ መገለጡ ጥሩ ነው። ከሁሉ በላይ ግን ፍጥረት ሁሉ በናፍቆት የሚጠብቁት በየትኛውም ቦታ በየትኛውም ጊዜ ሳንዛነፍ በፍቅር የምንገለጥበትን ጊዜ ይጠበቃሉ። የሁሉ ነገር መጠቅለያው፣ በምንሰራው ማንኛውም ነገር ውስጥ ስንጨምረው መልካም ተጽዕኖ የሚኖረው ፍቅር ነው።

በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ እግዚአብሔር አንድያ ልጁን እስከ መስጠት ድረስ ዓለምን እንዲሁ ወዶአልና፤ እግዚአብሔር ልጁን ወደ ዓለም የላከው በዓለም ለመፍረድ ሳይሆን፣ ዓለምን በእርሱ ለማዳን ነው። ዮሐንስ 3:16-17


እግዚአብሔር ሁልቀን የማይቀያየር ፍቅሩን በማሳየት እንድንገለጥ በፀጋው ይርዳን።